ህይወት?. . . . ክፍል 3
በፕላኔታችን ካሉት ታላላቅ የሃይማኖት ሰዋችና በጎ አድራጊዋች ማዘር ትሬዛ በከፍተኛ ደረጃ ስማችው ይወሳል፡፡ ህይወታቸውን ሙሉ ለበጎ አድራጎት ስራ ሰውተዋል ፡፡ የእርዳታ እጅ የሚያስፈልጋቸው ሰዋች ባሉበት ሁሉ ማዘር ቴሬዛ ደከመኝ ልረፍ ሳይሉ ይገኛሉ ፡፡ እያንዳንዷን ደቂቃ የተቸገረን ሲረዱ፡ የታረዘን ሲለብሲ ፡ የታመመን ሲያጽናኑ ሲጸልዩ ያሳልፋታል፡፡ ይህን ሁሉ በጎ ነገር ለአንድ ሰው አይበዛም ወይ ተብለው ሲጠየቁ ሁሉንም የሚያደርገው እግዚአብሔር ነው ለሱ ምን ይሳነዋል በማለት ይመልሳሉ፡፡ በሥራቸው ውጥን ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዋች ቢገጥማቸውም እግዚአብሔር በተአምሩ የታቀደውን እንደሚያሳካው ይናገራሉ ለእንደ ማዘር ቴሬዛ ዓይነት ቅዱሳን ህይወት ማለት እምነት ነው ብንል ያስሞደን ይሆን ?
በሃገራችንም በብጽዕነታቸው ብዙ የተባለላቸው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በአንድ ወቅት የኢትዮጲያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ነበሩ ፡፡ አማማታቸውም ከእምነቴ ፍንክች እልልም ብለው በረሃብ እራሳቸውን አዳክመው ነው ይባላል፡፡ ለእምነት ኖረው ለእምነት መሞትን እዚህ ላይ ያስተውላል፡፡
በዚህ ረገድ ባለፈው ኣመት ማገባደጃ ላይ በአሜሪካን ሀገር መሲህ ነኘ ተብሎ ሰለተበነሳው ኮሬሽን የህይወቱ ፍጻሜ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡ ሰዋችን በማሳመን ችሎታውና በመጽሐፍ ቅስ እውቀቱ ብዙዋችን ያሳተው ኮሬሽ በምፅአት ቀን የማጎን ህይወቱ ያለፈው በመቶዎች የሚዎጠሩ የሰዎችንና ሕጻናትን ሕይወት ይዞ ነው፡፡ ይህንን ምን ይሉታል?
ካለፈው ዓመት ድርጊቶች ሳንመጣ አንድ የአየርላንድ ከፍተኛ የሃይማኖት ሰው ብፁዕ ነው ሲባል ቆይቶ ከብዙ ዓመታት በኋላ ከአንዲ ሴ የወለደው ልጅ መኖሩን ጋዜጦች ሲያትቁ የተወሰነ ግዜ ዜናውን ሲያስተባብል ቆይቶ አልሆነ
ሌላው ወደ ላቴን አሜሪካ መኮብለሉስ ምን ስያሜ ያስጠዋል? በሃይማኖ መርባ ብዙዎ በህይወታቸው የቆሸሹትን ለዚህ የሃይማኖት ሰው ተብዬ ሲናዘዙ ቆይተው፣ ንስሃ ገብተው ብዙዎች ባለፈ ባገደመ ቁጥር … የሰይጣን ድል መንሻና የክብር መውረሻ … መስቀል ተሳልመው የኋላ የኋላ እምነቱን የካደ ሰው መሆኑን ሲያውቁ ግራ ሳይጋቡ ይቀራሱ?
እምነታቸውን ከደው በህይወታቸው የሸፈጡሰዎች ከራሳቸው ጋር እየተጣሉ ለመኖራቸው አሌያም አይባልም ቤተክርስቲያን የምታዘውና የአገልጋዮቹ ተግባር የማይገናኙበት ብዙ ጊዜ ተከስቷል፡፡ በአንድ ሃይማኖት ጥላ ስር ተሆኖ ግጭቱ ይፈፋማል፡፡ የእግዚአብሔር ቤትም ለተወሰኑ ከፍሎች ለማድረግ ሙከራዎችም ይታያሉ፡፡ በእግዚአብሔር ስም እንዲህ ዓይነት ነገር መፈፀሙ በጣም ያደናግራል፡፡ ለነገሩ እምነት ሲያስቀጣም ተሰተውታል ዋቢ መጥቀስ ቢያስፈልግ የፊሊፒንሱ ጳጳስ ማኒሊ ውስጥ በቀረበላቸው 666 የታርጋ ቁር ባላት የዲፕሎማቲክ መኪና በምንም ተአምር አልሳፈርባትም በማለታቸው በገንዘብ መቀጣታቸው እንደ ማስረጃ ሊቀርብ ይችላል? የሃይማኖት ሰው በህግ ሲዳኝ አስቲ አስቱት ግን ሕይወት ምንድን ናት?