ህይወት?        ክፍል 7

… አይ ጊዜ አይ ጊዜ… ብዮ ብጀምር ግዜን መወንጀል እንዳይመስልብኝ ፈራሁ በእርግ የልማት ክንውኖችም ሆኖ የጥፋት ድርጊቶች በጊዜ ውስጥ ያልፈው፡፡ ለልማቱ አስየው ሲባልለት ለጥፋት እርግማን አይቀርለትም፡፡

 

በዘመናችን ብዙ ጥሩ ነገሮች እንደታዩና እንደተከወኑ ሁለ መአቶችም ተከስተዋል፡፡ ለምሳሌም ያህል የአካባቢው አይር መሳሳትና መቀደድ በውጤቶም ኋይለኛውን የፀሐይ ጨረር ንዳድ በምድር እንዳንድ ቦታዎች ላይ የአየር መዛባትን እስከትሏል፡፡ የእርሻ መሬቶች ደርቀዋል፡፡ ብዙዎችም በእርዳታ እየተደገሙ ከረሃብ ድነዋል፡፡ ለድርቅ መስፋት የአዞን መቀድድ ድርሻ ያኑረው እንጂ ከቦታ ምክንያቶ ይለያያሉ፡፡ የተባይ፣ የአረም በሽታዎችም ከመከላከል አቅም በላይ በሆኑበት ቦታ ትንሽ የማይባል ጉዳት አድርሰዋል፡፡

 

በመሬት መንቀጥቀጥ፣ ጎርፍ ለመጥለቅለቅ፣ እሳት ቃጠሎ በመሳሰሉት ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮ ህይታቸው ያለፈው፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው፣ የእድሜያቸውን ያካበቱት ንብረታቸው የወደመባቸው፣ ቤተሰባቸው ተበትኖቻቸው የተሳቀቁ እጅት ብዙ ናቸው፡፡

 

አሳሳቢውና የሰው ልጆች አፈጣኝ መፍትሄ ሊያደርጉለት የሚባው ደግሞ ሰው ሰራሽ የአካባቢ ግጭቶችን በውይይት እንዲፈቀ ማድረግ ነው፡፡ በምስራቅ አፍር ጎረቤታችን በሆነቸው ሶማሊያ በመካሄድ ላይ ያለው የፖለቲካ ብጥብ ሀገሪቱን በሰው ህይውትና በኢኮኖሚ እያዳሸቃት ነው፡፡ ህዝቦቿም ወደ ጎረቤት ሀገሮች ስደት ተዳርገዋል በአንጉላ፣በደቡብ አፍረካና በዩዝላቪያ የተፋፋመ የእርስ በርስ እልቂ ችል ተብሎ ሊታይ አይገባውም፡፡ በእርግጥ አሁን በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው የፖለቲካ ፓርቲዎች ለነፃ ምርጫ ፉክክር ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም፡፡ ነገር ገን ከረጅም ዓመታት በፊት የተጫረውን እሳፈት ማጥፋት አለበት፡፡

 

የሰው ልጅ የኑሮ አቋም በበሽታውም ወገን በጣም አስከፊ ዕጣ ድርሶታል፡፡ ኤድስ፡፡ በሽታ ከተፈጥሮ ጋር የተቆራኝ መሆኑ ቢታወቅም የመስፋፋቱ ጉዳይ ግን ሰው ሰራሽ ነው ማለት የሚቻልበት ደረጃ ተደርሷል፡፡ ምክንያቱም የበሽታ መዛመቻ መንገዶችን በጸመለከጸ መግናኝ ብዙኃን ከመቼው ጊዜ በበለጠ ሁኔታ ተምህርታዌ መግለጫዎን፣ ማስታወቂያዎችን አሰራጭተዋል፡፡ በተለያዩ የበጎ አላማ ማህበራት በራሪ ወረቀቶችን … የህይወት ጃኬቶችን … እከፋፈለዋል፡፡ ነገር ገን አልፎ የሚነገረው የበሽተኞች ቁጥር መጠን ከፍ ለማት ግን የሰው ልጆች ለሚሰጡት ትምህርቶቸ ልቦናቸውን እንዳልሰጡ ያመለክታል፡፡

 

በአንድ ወቅት ከወደ ሩቅ ምስራቅ የተደመጠው ዜናም የሚዘገንን ነው፡፡ በህንድና በታይላንድ የኅህጻናት ሽያጭ፡፡ በለጋ ዕድሜያቸው ወደ ሽርሙጥና ዓለም የሚደረጉት ህጻናት ዓይናችውን ከፍቅረተንዋይ ያሳወራቸው አረመኔዎ ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳይቀጥልም መላው የሰው ልጅ በአጭሩ ለመቅጨት መፍትሔውን መሻት ያስፍልገዋል፡፡

 

ከኢጣሊያ ያለው የማፊያ ድርጅትም ለህግ ወጥ ድርጅቱ መበልጸግና የማሕበረሰቡን ሰላም ሰቆቃ እንዲመላበት ድርጅቱን አጥብቀው የሚቃወሙትን የፐሊስ ኃይሎች፣ የፍርድ ቤት ዳኞንና የመንግስትን ባለሥልናት በየቦው ከነቤትሰቦቻቸው እየፈጁና የህዝቡንም ሰላማዊ ኑሮ አያደፈረሱ ይገኛ፡፡ የኩልምቢያ የአደንዛዥ ዕፅ ተደጃሮች ከኢጣሊው ማፊያ ከሚያደርሰው በደል አይደለም እየፈፀሙ ያሉት፡፡

 

ባሁን ጊዜ ስላሎች ችግሮች ሙሉ በሙሉ መጥቀስ አባይን በጥፋት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ግን ህይወት ምንድን ናት?